ክፍለ ጊዜ 4

ኢየሱስ በመሞት ያከናወነውን ነገር በተመለከት ስንነጋገር ስለራሱ የተናገረውን ነገር ማመን ቃል ኪዳኖቹን ማግኘት እንደምንችል አይተናል፣ ሆኖም ግን ቃል ኪዳኖቹ በሕይወታችን ውስጥ እውን እንዲሆኑ ከተፈለገ፣ የአመለካከት እና የባህርይ ለውጥም ያስፈልገናል።

ለውጥ የሚጀምረው ስለ እራሱ ያለውን ነገር እና ስለ እኛ ያለውን ነገር በተመለከተ በማንበብ እና በማመን ነው። ኢየሱስ ስለ እኛ ከተናገረው ነገር ጋር ሲነጻጸር ስለ እራሱ የተናገራቸውን አንዳንድ ምሳሌዎች ከታች እንመልከት።

  1. ኢየሱስ ሙሉ በሙሉ መልካም ነው። እኛ በክፋት የተሞላን ነን።
  2. ኢየሱስ ወዶናል። እኛ ጠላነው።
  3. ኢየሱስ መረጠን። እኛ ገፋነው።
  4. ኢየሱስ እግዚአብሔርን በፍጹም ታዘዘው። እኛ በእግዚአብሔር ሕጎች ላይ አመጽን።
  5. ኢየሱስ እኛን ጨምሮ ለጠላቶቹ ሲል በፈቃዱ መከራን ተቀበለ። እኛ ለምንወዳቸው ሳይቀር መከራ መቀበልን አልፈቀድንም።
  6. ኢየሱስ ከሁሉ የላቀ አገልጋይ ነበር። እኛ ማገልገል ሳይሆን መገልገል ነው የምንፈልገው።
  7. ኢየሱስ ከሙታን ተነሳ። እኛ ወደ መቃብራችን እንወድቃለን፣ ቢሆንም ተስፋ አለ ምክንያቱም ኢየሱስ ሕይወቱን ሰጥቶናል።

ኢየሱስ አምላክ ቢሆንም እውነተኛ ሰውም ነው። በምድራችን የኖረ ከሁሉ የላቀ ሰው ነው፣ እና ጠላቶቹ ሳለን እኛን መውደድ እና ፍቅራችንን መፈለግ መረጠ።

በትህትና ካልቀረቡት በስተቀር ማንም ሰው በኢየሱስ መቀየር አይችልም። ኢየሱስ አስማት አይደለም። በአእምሯችን ውስጥ ያለን ሐሳብ ሁሉ የሚያውቅ ሰው ነው።

መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፣ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል ይላል። እኛ የምንፈልገውን ነገር ለማግኘት ብቻ ብለን ኢየሱስን ለመጠቀም ፈልገን ከቀረብነው በእሱ ተቀባይነት አይኖረንም። እራሳችንን ከክፋታችን ካልተመለስን እና ክፋታችንን መጥላት ካልጀመርን በስተቀር፣ እና በምትኩም የእሱን መልካምነት ካልመረጥን፣ እሱን ወይም የቃል ኪዳኑን ጥቅም ፈጽሞ አናውቅም።

ይህ በክፋት ላይ የመጸጸት ዝንባሌ፣ ለኢየሱስ መልካምነት ጥልቅ ምኞት እና በገባው ቃል ላይ ጥብቅ እምነት ማሳደር አዲሱ ልማድ ይሆናል። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እሱ ያለውን ስናነብ፣ ከዚያም ስንጸልይ እና የእሱን ፈቃድ ስንሻ አመለካከታችን ከትዕቢት ወደ ትሕትና ይቀየራል። እሱን መምሰል እንጀምራለን።

ኢየሱስ ልባችንን ያያል። ክፋትን መጥላትን ማሳደግ እና ክፋትን ለመተካት የእሱን ቸርነት መፈለግ አለብን። ከዚያ፣ ኢየሱስ ይቅርታ እንዲያደርግልን ስንጠይቀው ያደርግልናል።

በእውነተኛ ትሕትና ስንቀርበው ስብራታችንን ያውቃል እንዲሁም ልባችንን መጠገን ይጀምራል። እራሳችንን በሐቅ ማየት ስንጀምር እና እግዚአብሔር እኛን መውደድ እና የእሱን መልካምነት እንድናዳብር የመምረጡን እውነት ጋር አስማምተን ሕይወታችንን ስንኖር ነው እግዚአብሔር ሕይወት፣ ደስታ፣ እና ፍቅር የሚሰጠን።

እሱ በሂደቱ ውስጥ እኛን የሚያሳትፍበት መንገድ ውብ አይደለም?

በክፋትዎ ካፈሩ፣ መልካም ነው! ወደ እሱ ይሩጡ። በትሕትና ይንበርከኩ እና ስለራስዎ እውነት ስለገለጠልዎ ያመስግኑት። ይህ ኢየሱስ በፍቅር እየተከተልዎ ስለመሆኑ ማረጋገጫ ነው።

ከክፋትዎ ይመለሱ፣ ይልቁንም ወደ ኢየሱስ ይዙሩ። እራስዎን መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይቅበሩ። እራስዎን በጸሎት ውስጥ ይጥመቁ። ኢየሱስ ማን እንደሆነ እና በእርስዎ ውስጥ እና በእርስዎ አማካኝነት ምን ሊሰራ ቃል እንደገባ ያሰላስሉ። እሱን እንዲያስደስቱት እና ከእሱ ጋር በጥብቅ ወዳጅነት እንዲኖሩ ለእሱ ይገዙ። ንጹሕ ሕይወት ለመኖር ኃይልና ስልጣን የሚሰጡዎት የእሱ ፍቅር እና ቃል ኪዳኖች እንደሆኑ ያስታውሱ።

ይህ ቋሚ የእለት ተእለት ሂደት ነው። ሳይሳካልዎ ሲቀር፣ በጸጸት ወይም በተስፋ መቁረጥ ስሜት አይጠመዱ። ያልተሳካልዎ ጊዜ ከመቸውም ጊዜ የላቀ ወደ እግዚአብሔር መመለስ ያለብዎት ጊዜ ነው። ክፋትዎ ከእግዚአብሔር የበለጠ ኃያል ነው የሚለው ሐሳብ የማይረባ እና የትዕቢት ነው። ኢየሱስ እሱን በመቃወም ሲኖሩ ይወድዎ ነበር። በእርግጥ አሁን የእሱ ልጅ ስለሆኑ ይቅር ይልዎታል! እሱ ከክፋትዎ የበለጠ ብርቱ ሲሆን እሱ እርስዎ ራስዎን ከሚጠሉት በላይ ይወድዎታል። ያንን ይመኑና ተስፋ አይቆርጡም።

ጠለቅ ይበሉ

1ኛ ዮሐንስ 1፣ ኤፌሶን 5:8 እና ዮሐንስ 11:9-10ን ያንብቡ፤ ከዚያም ስለ ይቅር ባይነት ያለዎትን ግንዛቤና "በብርሃን ውስጥ መመላለስ" ማለት ምን ማለት እንደሆነ ይጻፉ። ስለዛ ይጸልዩ፣ ከዚያ ከታማኝ ክርስትያን ጓደኛ ጋር በሐቅ ይወያዩ። በብርሃኑ ውስጥ እየተመላለሱ ነው? ካልሆነ ወደ ብርሃኑ ለመግባት ዛሬ ምን ለውጥ ማድረግ ይችላሉ?

ያለፈው ዝርዝር ዝርዝር ቀጣይ