ክፍለ ጊዜ 5

ከክፋት ርቀን ወደ እግዚአብሔር ስንቀርብ፣ እሱ ሕይወታችንን መቀበል ይጀምራል። እሱ ሕይወታችን ይሆናል። ደስታችን። እሱ የሕይወት አመለካከታችንን ይቀይራል። መጽሐፍ ቅዱስ ይህንን ሂደት አእምሯችንን ማደስ ይለዋል።

መጽሐፍ ቅዱስ ይህንን ለውጥ የሚያብራራባቸው ሦስት ዋና መንገዶች እሱን በሦስት የተለያዩ ሚናዎቹ በመጥራት ነው፦ አዳኝ፣ ጌታ፣ እና ወዳጅ።

መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ ከመሞቱ በፊት እና በኋላ ሰው እንደነበረ ለእኛ ለማሳየት ከፍተኛ ጥንቃቄ ያደርጋል። ደቀመዝምሮቹን እና እሱን የወደዱትን ሰዎች "ወዳጆች" ይላቸዋል።

ኢየሱስ ከሙታን ከተነሳ በኋላ ለገደሉት ሰዎች ምን ያህል እንደተሳሳቱ አላሳያቸውም። ይልቁንም ለወዳጆቹ ቁርስ ሰራላቸው፣ ከዚያ ከእነሱ ጋር ተጓዘ እና እራት አብሯቸው በላ። በሌላ ታሪክ፣ ቤት ውስጥ ለወዳጆቹ ተገለጠላቸው፣ ጠባሳዎቹን አሳያቸው እና ከእነሱ ጋር በላ።

ወደ ምድር የመጣበት ዋነኛ ዓላማ ለመወዳጀት እንደሆነ ማሳየት ነበር የፈለገው።

የሁሉንም ነገር አምላክ የሆነው ወዳጆቼ ብሎ ጠራን። እኛ እንደምናገለግለው እና እንደምንወደው እሱም ያገለግለናል ይወደናል። እኛ ውስጥ በማይሰበር ወዳጅነት ኖሯል። እርስ በራሳችን እንዋደዳለን እንከባበራለን።

ከወደዱት እና ስለእራሱ የሚለውን ነገር ካመኑ፣ ከራስዎ ክፋት ይመለሳሉ እንዲሁም በሕይወትዎ ውስጥ የእሱን ፍቅር እና ኃይል ያጣጥማሉ።

በእርግጥ እኛ ወዳጅነቱን እንድናጣጥም፣ እርሱ ከክፉ ነገር ሊያድነን እና የሕይወታችን ማእከል ሊሆን ያስፈለገዋል። አዳኛችን በመሆኑ ያለማቋረጥ ይቅር ይለናል ነጻ ያወጣናል። ያንን በቀደሙት ክፍለ ጊዜዎች ላይ ተመልክተነዋል።

ኢየሱስ ጌታ ስለመሆኑስ?

ጌታ ማለት በስልጣን የሚመራ ሰው ነው። እሱ "ይህንን አድርጉ" ሲል አገልጋዮቹ ይታዘዛሉ። መጽሐፍ ቅዱስ እሱ የእኛ ጌታ ለመሆን ይጠይቃል ይላል። ይህ ከእሱ ጋር በወዳጅነት ለመኖር ቅድመ ሁኔታ ነው።

አይደናገሩ፡፡ ጥርሳችንን እንድንነክስ እና እንድንታዘዝ አይፈልግም። እግዚአብሔር ለዘመናት ጥርሳቸውን ነክሰው በታዘዙት ብዙ ሰዎች ሲቆጣ ኖሯል። ይልቁንም እግዚአብሔር ሰዎች እንዲታዘዙት የሚፈልገው እሱን ለማስደሰት ስለፈለጉ ነው። እሱ ሕይወታችንን እንድንሰጠው የሚፈልገው በእውነተኛ ፍቅር እና እምነት እንጂ መስጠት ስላለብን አይደለም።

ሊታዘዙት እና ሕይትዎን ሊሰጡት ካልፈለጉ እራስዎን በቃሉ (በመጽሐፍ ቅዱስ) ውስጥ ይንከሩ እና እሱ ማን እንደሆነ፣ እሱ እርስዎ ማን ነዎት እንደሚል እና ለእርስዎ ምን እንዳደረገልዎ ያስቡ። ከዚያ ለእሱ ያልዎትን መሻት በንቃት ይከተሉ።

የተመኙትን ሰው እንዴት እንደሚከተሉ አስመልክቶ የገሃዱ ዓለም ምሳሌ እነሆ። ፍቅረኛሞች ሲጋቡ አንዳቸው ለሌላው ሁልጊዜ ፍቅር አይኖራቸውም። ሆኖም ግን እርስ በራሳቸው በደግነት ሲተያዩ አንዳቸው ለሌላው ያላቸው ፍቅር ያድጋል።

አንዲት ሚስት ለባሏ ስጦታ ትወስዳለች፤ እና ስጦታውን አንድ ላይ ስትሰበስብም ደግነቱን ታስታውሳለች። ካርዱን የማቀድ፣ የመግዛት እና የመሙላት ቀላል ተግባር ለእሱ ያላትን ፍቅር እንድትከተል ይረዳታል፣ ምክንያቱም እሱ ማን እንደሆነ ስታስታውስ እና ምላሽ ስትሰጥ ፍቅር በልቧ ያድጋል እንዲሁም በእርሱ ላይ በሚኖራት እምነት አማካኝነት እውነት ይሆናል።

ኢየሱስ ማን እንደሆነ እራሳችንን ስናስታውስ እና ለእኛ ያለውን ቸርነት ስናስብ ፍቅር በልባችን ያድጋል እንዲሁም እውነት ይሆናል። በምላሹ ምኞቶቻችንን ይቀይራል፣ እናም በፍቅር እና ማን እንደሆነ በማመን እንድንታዘዘው ጥንካሬ ይሰጠናል።

የእግዚአብሔር ቃል ኪዳኖች በሕይወታችን እውን እንዲሆኑ ቃሉን በማንበብ፣ በመጸለይ እና ትእዛዛቱን በማመንና በማክበር ለእሱ ያለንን ፍቅር መከተል አለብን። እሱን እንደ አዳኛችን፣ ጌታችን፣ እና ጓደኛችን በፈለግነው ቁጥር ያ ሁሉ አስተሳሰባችንን ይቀይረዋል።

እነዚህ ሂደቶች እግዚአብሔር ማንነታችንን ለመቀየር የሚጠቀመው እነሱን ስለሆነ ወሳኝ ናቸው። ማንነታችንን የሚያድሰው አዳኝ፣ ጌታ፣ እና ወዳጅ የመሆኑ ማንነት ላይ ባለን እምነት አማካኝነት ነው።

ጠለቅ ይበሉ

ቆላስይስ 1:15-23ን ያንብቡና ኢየሱስን ለመከተልና አዳኝ፣ ጌታ፣ እና ወዳጅ ብሎ ለመጥራት የወሰኑት ለምን እንደሆነ ያልሰሙትን የሚወዷቸውን ሰዎች ስም ይጻፉ። እግዚአብሔር ልባቸውን እንዲከፍትላቸው እና እግዚአብሔር እንዴት ህይወትዎን እንደለወጠ ታሪክዎን ለማካፈል እድል እንዲሰጥዎ ይጸልዩ። እሱ እርስዎ ያልተጠቀሙባቸውን ዕድሎች እየሰጥዎት ነው?

ያለፈው ዝርዝር ዝርዝር ቀጣይ